Tuesday, May 24, 2016

...በኔዘርላንድ ሀገር ውስጥ እስር ቤቶች እየተዘጉ ነው የተዘጉም አሉ ....


......ሁሉም ድርሻውን ከተወጣ እዚህም ይደረሳል...
...የገረመኝ ነገር...ግን እንዴት ሊሆን ይችላል?
ለነገሩ አፍሪካ ውስጥ ተወልጄ እንደዚህ ብጠይቅ አትፍረዱብኝ ሁሉም ጉልበተኛ ኑሮውም ጉልበቷ እኛላይ... ብቻ ይሁን... ተመስገን ነው እኛም እንበረታባታለን... የቀደሙት ፍቅርን ዘርተው አለፉ አባቶቻችን ደግሞ አጭደው በሉ  ለእኛም ሳይዘሩልን እምነትና ተስፋን ብቻ ሰጥተውን  አለፉ እኛ ይኸው በፍቅር እጦት እንራባለን በእምነት እና ተስፋ እንጓዛለን  ሁሉም እጃችን ላይ ሆኖ እንቸገራለን...  እኛስ እሺ የቀደሙት አባቶችንን ትዝታም ያጥግበን ልጆቻችንስ?
...አይደለም ከአውድማው ከነመፈጠሩ ፍቅር ስለመኖሩ ለሚጠራጠሩት? እምነት እና ተስፋ ላጡት...  እናስብበት... ለኛ ቢያልፍ ቢረፍድ እንኳን  ለልጆቻችን ለቀጣይ ትውልድ እናስብ...  ይህንን ደግሞ የሁሉም የሁላችንም ድርሻ ነው።.... እምነትና ተስፋ ከነዚህም በላይ ፍቅርን እናውርስ እንዝራ። ... ፍቅር ከሁሉም በላይ ...  የሰው ልጅ የሚበላውን ነው የሚመስለውና ፍቅርን እንመገብ ..... እናስተውል  ሁልጊዜም ከክፋት ደግነት ....ከጥላቻ ፍቅር ....ከጸብ እርቅ ....ከክርክር መስማማት ይሻላል... ወደ ራሳችን ወደ ቀደመው ነገር እንመለስ ... ያኔ እስር ቤት አይደለም ፍርድ ቤት ይዘጋል....
         ....ዲ. ብልሃት በላይ
          ......ግንቦት 15 2008 ዓ.ም....

http://www.techinsider.io/dutch-prisons-are-closing-2016-3?utm_content=buffer57f40&utm_medium=social&utm_source=facebook.com&utm_campaign=buffer-ti

No comments:

Post a Comment