Monday, May 23, 2016

" ማንም። እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል?" (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4:20)

እግዚአብሔር ይወደናል ፍቅሩን ለመግለጽ ሁሉን ሰጥቶናል። የሰጠንንም ሁሉ ይፈልጋል እኛ ምንም ሳናጓድል ከነትርፉ ልንሰጥ ግድ ይለናል..ነገር ግን እኛ በተንኮል ተውጠን በክፋት ታስረን እርሱ በነጻ የሰጠንን እኛ በጉልበት ያገኘነው ይመስል እንጓዛለን... ንጹህ ፍቅር በነጻ ሰጠን ማስተዋልንን  ከጥበብ ጋር አደለን ሙሉ ተስፋን በእምነት ውስጥ አስቀመጠልን... እናም..... እንዲሁ እንዳያችሁት እንዲሁ ይመለሳል ተብሏልና አሁንም ይመጣል እንደ ቀድሞ ለፍቅር ሊ'ቀጣ ሳይሆን ስለ ፍቅር ሊቀጣን ነው።  አዎ ሁላችንም ልንረዳው የሚገባ ነገር እግዚአብሔር ይቅር ባይ ነው ፍቅር ነው ይህ የእርሱ የባህሪው መገለጫ ነው ነገር ግን ይህንን ስናጎድል ስለፍቅር እንድናስተካክለው ይለምነናል ብዙ ምርጫዎች ይሰጠናል  ካልቻልን ግን  ቅጣቱን ሊሰጥ  ይመጣል... አዎ እርስ በርስ እንድንዋደድ አንዳችን የአንዳችንን በደል እንድንሸፍን እንድንረዳዳ አዞን ሄዷልና...  የሰጠንን ጥያቄ በግልጽ  ተቀምጧል
...ተርቤ አበላችሁን? ተጠምቼ አጠጣችሁኝ ?ታርዤ አለበሳችሁኝ? ታስሬ ጠየቃችሁኝ?.... እኚህ ጥያቄዎች ስናስተውል እርሱን ከእኛ ጋር እኩል የሚያደርገው እንደውም የሚገርመው ከእኛም ትንንሾች ጋር ያስቀምጣል ከታናናሾቹ ለአንዱ ካደረጋችሁ ለእኔ እንዳደረጋችሁ ነው (ማቴ 25)... ፍቅሩ ምነኛ እጅግ ይደንቃል ሁልም ጊዜ ለእኛ  ያደላልና... 
....ኦ አምላኬ ሆይ ምነኛ እራስህን ስለፍቅር አወረድከው እራስህን አሳልፈህ ሰጠኸን ... አምላኬ ሆይ የእራሴን በደል ብቻ እያሰብኩኝ የእራሴን ሀጢያት ብቻ እየተመለከትኩኝ የምጸጸትበትን ሌላውን በችግሩ በውድቀቱ ሰዓት የምረዳበትን በመንገዱም የማግዝበትን ወደ አንተ ቤት የማቀርብበትን በችግሩ የምረዳበትን።... ስለእራሴ በደል እንጂ ስለሌላው የማላይበትን አስተዋይ ልብ ስጠኝ .... በዛ በፍርድ ሰዓት ለምጠየቅው ጥያቄ መልስ ይህ ነውና።
  .......ዲያቆን ብልሃት በላይ
  .......ግንቦት 14

No comments:

Post a Comment